በምሁርና አክሊል ወረዳ ኢዜማ እያደረገ ላለው የምርጫ 2013 ዘመቻ ድጋፍ

  • US$10.00
    raised of $2,000.00 goal goal
0% Funded
1 Donors

The campaign owner has stopped the page from accepting further donations. Please contact them if you'd still like to donate

Help this ongoing fundraising campaign by making a donation and spreading the word.
Show more
Show less

የኢትዮጵያ ዜጎች ለማህበራዊ ፍትህ (ኢዜማ) በመጨው ምርጫ 2013 በጉራጌ ዞን የምሁርና አክሊል ወረዳ ህዝብ በየዘርፉ የገጠሙት ተግዳሮቶች በሚመለከተው አካል በትክክል ተሰምተው እንዲፈቱ አይነተኛ ድምጽ የሚሆኑ የህዝብ ተወካዮች ም/ቤትና የክልል ም/ቤት እጩዎችን አቅርቧል። ለዘመናት እዚያው ጉያው ስር ሆነው ህዝቡን በሙያቸውና በእውቀታቸው እያገለገሉ የቆዩት የኢዜማ እጩዎች አያደረጉት ባሉት የምረጡኝ ዘመቻ ለሚያስፈልጋቸው እንቅስቃሴና ወጪ የበኩልዎን አስተዋጽኦ እንዲያደርጉ በትህትና እንጠይቃለን።

በአገራች ብዙ ቦታዎች በሆነው መልኩ በምሁርና አክሊል ወረዳም እንዲሁ የገዥው ፓርቲ እጩዎች ብዙ የመንግስት ቁሳቁስና መጓጓዣን ጭምር በመጠቀም ቅስቀሳ ማድረግ እንደሚችሉ ይታወቃል። በአንጻሩ የኢዜማ እጩዎች የምርጫ ዘመቻውን የሚደጉሙት በአብዛኛው በግለሰብ ደረጃ ከሚያገኙት የወር ደመወዝ እንዲሁም ከአርሶ አደሩ ከሚሰበሰብ አነስተኛ መዋጮ ነው። በመሆኑም የምርጫውን ዝግጅት ፍትሐዊ በማድረግ የማህበረሰቡን ችግሮች ለመፍታት በሚጠቅም መልኩ የተጀመረውን ዴሞክራሲያዊ የሐሳብ ፉክክር የሚያነቃቃ መጠነኛ ድጋፍ ማድረግ ያስፈልጋል።

ለሀገራችንም ሆነ ለወረዳችን ወሳኝ በሆነው በዚህ ምርጫ በወረዳችን ተወላጆች ለኢዜማ የሚደረግ አስተዋጽኦ ትልቅ ታሪካዊ ትርጉም ይኖረዋል። ይህንን በማድረግ በሚፈለግ ጊዜ ከማህበረሰቡ ጎን በመቆምዎ የምሁርና አክሊል ወረዳ የኢዜማ አባላትና ደጋፊዎች በመራጩ ህዝብ ስም ከወዲሁ ከፍ ያለ ምስጋናችንን እናቀርባለን።

Organizer

  • Muhir Aklil EZema Support
  •  
  • Campaign Owner

Donors

  • Anonymous
  • Donated on Apr 11, 2021
Amount Hidden

No updates for this campaign just yet

Donors & Comments

1 donors
  • Anonymous
  • Donated on Apr 11, 2021
Amount Hidden

Followers

0 followers
No Followers Just Yet...
US$10.00
raised of $2,000.00 goal
0% Funded
1 Donors

No more donations are being accepted at this time. Please contact the campaign owner if you would like to discuss further funding opportunities

Help this ongoing fundraising campaign by making a donation and spreading the word.

Not Ready to Donate?

Did you know a 10 second Facebook share raises an average of $25?

Share on Facebook