በምሁርና አክሊል ወረዳ ኢዜማ እያደረገ ላለው የምርጫ 2013 ዘመቻ ድጋፍ
Fundraising campaign by
Ezema Muhir Aklil Support
-
US$705.00raised of $2,000.00 goal goal
Campaign Story
የኢትዮጵያ ዜጎች ለማህበራዊ ፍትህ (ኢዜማ) በመጨው ምርጫ 2013 በጉራጌ ዞን የምሁርና አክሊል ወረዳ ህዝብ በየዘርፉ የገጠሙት ተግዳሮቶች በሚመለከተው አካል በትክክል ተሰምተው እንዲፈቱ አይነተኛ ድምጽ የሚሆኑ የህዝብ ተወካዮች ም/ቤትና የክልል ም/ቤት እጩዎችን አቅርቧል። ለዘመናት እዚያው ጉያው ስር ሆነው ህዝቡን በሙያቸውና በእውቀታቸው እያገለገሉ የቆዩት የኢዜማ እጩዎች አያደረጉት ባሉት የምረጡኝ ዘመቻ ለሚያስፈልጋቸው እንቅስቃሴና ወጪ የበኩልዎን አስተዋጽኦ እንዲያደርጉ በትህትና እንጠይቃለን።
በአገራች ብዙ ቦታዎች በሆነው መልኩ በምሁርና አክሊል ወረዳም እንዲሁ የገዥው ፓርቲ እጩዎች ብዙ የመንግስት ቁሳቁስና መጓጓዣን ጭምር በመጠቀም ቅስቀሳ ማድረግ እንደሚችሉ ይታወቃል። በአንጻሩ የኢዜማ እጩዎች የምርጫ ዘመቻውን የሚደጉሙት በአብዛኛው በግለሰብ ደረጃ ከሚያገኙት የወር ደመወዝ እንዲሁም ከአርሶ አደሩ ከሚሰበሰብ አነስተኛ መዋጮ ነው። በመሆኑም የምርጫውን ዝግጅት ፍትሐዊ በማድረግ የማህበረሰቡን ችግሮች ለመፍታት በሚጠቅም መልኩ የተጀመረውን ዴሞክራሲያዊ የሐሳብ ፉክክር የሚያነቃቃ መጠነኛ ድጋፍ ማድረግ ያስፈልጋል።
ለሀገራችንም ሆነ ለወረዳችን ወሳኝ በሆነው በዚህ ምርጫ በወረዳችን ተወላጆች ለኢዜማ የሚደረግ አስተዋጽኦ ትልቅ ታሪካዊ ትርጉም ይኖረዋል። ይህንን በማድረግ በሚፈለግ ጊዜ ከማህበረሰቡ ጎን በመቆምዎ የምሁርና አክሊል ወረዳ የኢዜማ አባላትና ደጋፊዎች በመራጩ ህዝብ ስም ከወዲሁ ከፍ ያለ ምስጋናችንን እናቀርባለን።
Organizer
- Ezema Muhir Aklil Support
- Campaign Owner
Donors
- Anonymous
- Donated on Apr 18, 2021
- Anonymous
- Donated on Apr 16, 2021
- Anonymous
- Donated on Apr 15, 2021
No updates for this campaign just yet
Donors & Comments
- Anonymous
- Donated on Apr 18, 2021
- Anonymous
- Donated on Apr 16, 2021
- Anonymous
- Donated on Apr 15, 2021
- Anonymous
- Donated on Apr 15, 2021
- Anonymous
- Donated on Apr 15, 2021
Hppy to contribute my part in this effort. E-Zema representative, esp. Bartema need support.
- S K
- Posted On Apr 15, 2021
ኤዜማ ከተመረጠ እንደምርጫ ምልክቱ ለሁሉም ዜጋ ሚዛናዊ የሆነ ስራ ይሰራሉ ብለን እናምናለን ። ለማህበረሰባችን በጣም ብዙ መሠረታዊ አገልግሎቶች እስካሁን አልተሟሉም ። ከእነዚህ ዋናው መንገድ ነው። ኢዜማ እድሉ አግኝቶ ከተመረጠ የመንገዱ ነገር አንድ መላ ያመጣሉ ብለን እንጠብቃለን ። የባርጠማም ግቤና ይቅናን።
- Anonymous
- Donated on Apr 15, 2021
ከተመረጠ እንደ ምርጫ ምልክቱ ኢዜማ ለሁሉም ዜጋ ሚዛናዊ የሆነ ስራ ይሰራል ብለን እናምናለን ። ለማህበረሰባችን በጣም ብዙ መሠረታዊ አገልግሎቶች እስካሁን አልተሟላም ። ከእነዚህም ዋነኛው መንገድ ነው። ኢዜማ እድሉ ካገኘ የመንገዱ ነገር መላ ይፈልጋሉ ብለን እናምናለን ። የባርጠማም ዘበንዌ ይዕናን።
- Guest
- Donated on Apr 14, 2021
- Anonymous
- Donated on Apr 14, 2021
የኢዜማ ሀሳብ ለመላው አገራችን ብቻ ሳይሆን ለወረዳችንም እንዲሁ በጅጉ የሚጠቅም ነው። በተለይ የምሁርና አክሊል ነዋሪ የሚገጥመውን ችግር ከህዝቡ ጋር እየዋላችሁና እያደራችሁ በቅርበት በመረዳት የሚፈታበትን ሀሳብ ስታፈልቁ የነበራችሁ የኢዜማ እጩዎች እና አባላት ለወረዳው ታስፈልጉታላችሁና በርቱ!